Tag: Ethiopia Economy

ልማት ባንክ ከቀውስ አገግሜያለሁ አለ ፤ ያልተመለሰ የብድር ምጣኔውን በግማሽ ዝቅ አድርጌያለሁ ብሏል

ዋዜማ – ለበርካታ አመታት ባልተመለሰ ብድር ምጣኔ መናር ብሎም በብልሹ አሰራር በቀውስ ውስጥ የከረመው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከረጅም ጊዜ በኋላ ባልተመለሰ ብድር ምጣኔ ከፍተኛ የሚባል መሻሻልን ማስመዝገቡን ለዋዜማ ተናግሯል። የባንኩ…

መንግስት 15 ቢሊየን ድጎማ አድርጌበታለሁ ያለው ማዳበርያ በነጋዴዎች በኩል ለገበሬው በውድ ዋጋ እየተሸጠ ነው

ዋዜማ- እንደ ነዳጅ ሁሉ የመንግስት ከፍተኛ ድጎማ ተደርጎበታል የተባለው ማዳበሪያ በህብረት ስራ ዩኒየኖች እና በገበሬ ማህበራት በኩል ለአርሶ አደሩ ከመድረስ ይልቅ ግልጽ ባልሆነ መንገድ በነጋዴዎች እጅ እንደተከማቸ ዋዜማ ከተለያዩ ምንጮች…

የገንዘብ እጥረት ውስጥ የገቡ ባንኮች በከፍተኛ ወለድ ቁጠባ መሰብሰብ ጀምረዋል

ዋዜማ – ከጥቂት ወራት ወዲህ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት ውስጥ የገቡት የግል ባንኮች ቁጠባቸውን ለማሳደግና በቂ መንቀሳቀሻ ገንዘብ ለማግኘት ከፍተኛ ገንዘብን በጊዜ ገደብ ቁጠባ (Fixed time deposite) ሊያስቀምጡ ለሚችሉ ደንበኞች ከፍተኛ…

በቀጣዩ በጀት አመት አዳዲስ የመንግስት ሰራተኛ ቅጥር እንደማይፈጸም የገንዘብ ሚንስትር አስታወቀ

ዋዜማ- መንግስት ከአንድ ወር በኋላ ሃምሌ 2015ዓ.ም በሚጀምረው አዲሱ የ2016 ዓ.ም በጀት አመት ምንም አይነት የመንግስት ሰራተኛ ቅጥር እንደማይፈጸም የገንዘብ ሚንስቴር አስታወቀ፡፡ የገንዘብ ሚንስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ከጥቂት ቀናት በፊት…

የፌዴራል እና ክልል ተቋማት በበረታ በጀት እጥረት ውስጥ ወድቀዋል

ዋዜማ- በዚህ አመት በተለየ ሁኔታ የፌዴራል እና የክልል መንግስት ተቋማት በከባድ የበጀት እጥረት እየተፈተኑ መሆኑን ዋዜማ ያሰባሰበችው መረጃ ያሳያል። በዚህም ሳቢያ ለበርካታ ፕሮጀክቶች መከፈል የነበረበት ገንዘብ አልተከፈለም። የወጡ የግዥ ጨረታዎች…

የጠቅላይ ሚንስትሩ የቤተመንግስት ፕሮጀክት ለሶስት ተቋራጮች ተሰጠ

ዋዜማ- የ”ጫካ” ፕሮጀክት የሚል ስያሜ ላለው እና ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በቅርበት ለሚከታተሉት የአዲስ ቤተ መንግስት ግንባታ ተጨማሪ ሶስት ተቋራጮች መቀጠራቸውን ዋዜማ ከሁነኛ ምንጮቿ ሰምታለች። ከቤተ መንግስት በተጨማሪ ፣ የቅንጡ…

የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የጠራው የ”ደሞዝ ይሻሻል” ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ

ዋዜማ ራዲዮ- ለዓለም አቀፍ የሰራተኞች ቀን ዛሬ ሚያዚያ 23 ቀን 2015 ዓ.ም የተጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ በመንግስት ክልከላ ምክንያት እንደማያካሂድ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን አስታወቀ። ኮንፌደሬሽኑ ለጋዜጠኞች በላከው መግለጫ እየተባባሰ ከመጣው…

ስጋ አምራችና ላኪዎች ከዛሬ ጀምሮ ምርት መላክ እናቆማለን አሉ

ዋዜማ- መንግስት በስጋ ላኪዎች የስራ ዘርፍ እየተባባሰ የመጣውን የውጪ  ምንዛሪ ስወራ ማስቆም ስላልቻለ ስጋ ወደ ውጪ ሀገር እንደማይልኩ አስታወቁ።  በውስጡ አስር ዋና ስጋ አምራችና ላኪ ኩባንያዎችን የያዘው ፣የኢትዮጵያ ስጋ አምራችና…