Month: February 2023

በአዲስ አበባ ላይ “ውድመት” ሊያስከትል ይችላል የተባለውን ኬሚካል ከ2 ዓመት በኋላም ማስወገድ አልታቻለም

ከሁለት ዓመት በፊት በአዲስ አበባ ላይ “ዕልቂትና ውድመት”  ሊያስከትል ይችላል የተባለ የኬሚካል ክምችት መኖሩን መንግስት ራሱ አስታውቆ ነበር። ይህ አደገኛ የኬሚካል ክምችት አሁንም መፍትሄ አላገኘም። ዋዜማ ለምን ችግሩን ማስወገድ አልተቻለም? …

ስንዴ በሀገር ውስጥ በኮንትሮባንድ በውድ ዋጋ እየተሸጠ ነው

ዋዜማ- በቅርቡ መንግስት የስንዴ ምርትን ለውጪ ገበያ ማቅረብ መጀመሩን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ በሀገር ውስጥ የስንዴ ዋጋ በከፍተኛ መጠን የናረ ሲሆን ህገ ወጥ የኮንትሮባንድ የስንዴ  ግብይት መጀመሩን ዋዜማ ከአርሶአደሮችና ከሸማቾች ያሰባሰበችው…

ሰሞኑን ከ83ሺ በላይ ተፈናቃዮች ከሶማሌላንድ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል

ዋዜማ- ባለፉት ሳምንታት በሱማሌላንድ ላስ አኖድ ከተማ የተቀሰቀሰውን ግጭት የሸሹ ከ83ሺ በላይ ስደተኞች የኢትዮጵያን ድንበር በማቋረጥ ሶማሌ ክልል ዶሎ ዞን እንደሚገኙ የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት አስታውቋል። ከእነዚህም ውስጥ አብዛኞቹ ሴቶች፣ህፃናት፣ነፍሰ…

የአማራ ክልል በሰሜኑ ጦርነት በደረሰው ውድመት ለመልሶ ማቋቋም 475 ቢሊየን ብር ያስፈልገኛል አለ

ዋዜማ-  የአማራ ክልል በሰሜኑ ጦርነት በመሰረተ ልማትና በዜጎች ላይ ከደረሰው ውድመት ለማገገምና መልሶ ለመገንባት በድምሩ 475 ቢሊየን ብር ያህል እንደሚያስፈልገው  ለዋዜማ ተናግሯል።  በአማራ ክልል በጦርነት የተጎዱ አከባቢዎች መልሶ ማቋቋምና ግንባታ…

የአዲስ አበባ መስተዳድር ለበላይ አመራርሮች አዲስ  የጥቅማ ጥቅም ድጎማ አዘጋጀ

ዋዜማ- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማው ለሚገኙ የተለያዩ ተቋማት አመራሮች አዲስ የጥቅማ ጥቅም መመሪያ ማጽደቁን ዋዜማ ሰምታለች። መመሪያው በከተማ አስተዳደሩ ስር ያሉ ቢሮዎች ፣ኤጀንሲዎች ፣ ክፍለ ከተማ እና ወረዳ ውስጥ…

የፀጥታና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ባለሀብችን ለመሳብ እንቅፋት እንደሆኑበት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

ዋዜማ- የፀጥታ፣ የመልካም አስተዳደርና የውጪ ምንዛሪ ዕጥረት  ችግሮች የውጪ ባለሀብቶችን በበቂ ለመሳብ እንቅፋት እንደሆኑበት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።  የውጭ  ጉዳይ ሚንስቴር የ2015 ዓ.ም የስድስት ወራት አቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ጥር 24…

የቤተክርስቲያኒቷ ህጋዊ መብት ካልተከበረ ሲኖዶሱ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚጠራ አስጠነቀቀ

ዋዜማ- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ሲኖዶስ መንግሥት ለቤተክርስቲያኗ ሕግ የማያስከብርላት ከሆነ፣ “ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ” የቤተክርስቲያኗ መብት እስኪረጋገጥ እንደሚታገል ዛሬ ማምሻውን በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ሲኖዶሱ፣ የቤተክርስቲያኗ መብት እስኪረጋገጥ ከፓትርያርኩ ጀምሮ ሁሉም…

አዲሱ የብሄራዊ ባንክ ገዥ ዛሬ ከፋይናንስ ዘርፍ ባለድርሻዎች ጋር ይመካከራሉ

ማሞ ምህረቱ ባለፉት አራት አመታት በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ውሳኔዎች ላይ በማማከርና ፖሊሲ በማዘጋጀት ቁልፍ ሚና ነበራቸው። አሁን የብሔራዊ ባንኩ ገዢ ሆነው ተሹመዋል። የዋጋ ግሸበት፣ የገንዘብ ፖሊሲ፣ የውጪ ዕዳ እና በቀጣይ…