Tag: Tigray

በአማራና በትግራይ ተፈናቃዮች “ተርበናል” እያሉ ነው

መንግስት ዕርዳታ እያቀረብኩ ነው ብሏል ዋዜማ – የኢትዮጵያ መንግስት ከዕርዳታ ጥገኝነት ለመውጣት ዘመቻ በጀመረበት፣ የአሜሪካ መንግስት ከፍ ያለ የገንዘብ ድጋፍ ባቋረጠበት በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ ተፈናቅለው በመጠለያ የሚገኙ ዜጎች የረሀብ ፈተና…

የኤርትራ ናቅፋ ከድንበር አካባቢዎች ወደ ትግራይ ገበያ ዘልቆ እየተሰራጨ ነው

ዋዜማ- በኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር አካባቢዎች ተገድቦ የነበረው የኤርትራ መገበያያ ገንዘብ ናቅፋ ከኮንትሮባንድ ንግድ ጋር ተያይዞ ወደ ሌሎች ከተሞችም በስፋት እየተሰራጨ መሆኑን ዋዜማ ከነዋሪዎችና በንግድ ስራ ላይ ከተሰማሩ ግለሰቦች ካሰባሰበችው መረጃ…

በኢፈርት ኩባንያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው የባንክ ሂሳብ እግድ ተነሳ

ዋዜማ- በትግራይ መልሶ ማቋቋም ኢንዶውመንት ፈንድ (ኢፈርት) ስር በሚንቀሳቀሱ 22 ኩባንያዎች የባንክ ሂሳብ ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ መነሳቱን ዋዜማ ሰምታለች፡፡ በተቋሙ ኩባንያዎች የባንክ ሂሳብ ላይ የተጣለውን እግድ በሚመለከት አሰራርን በተከተለ…

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አግዶት የቆየውን የማእድን ቁፋሮ ዳግም ሊያስጀምር ነው

ዋዜማ-የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አግዶት የቆየውን የማእድን ማውጣት ስራ ለማስጀመር የሚያስችል አዲስ መመሪያ አወጣ፡፡ ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ተቋርጦ የነበረውን ማዕድን የማውጣት ስራ ዳግም ለማስጀመር የሚያስችል አዲስ መመሪያ…

እገታ ፣ግድያና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ በራያ አወዛጋቢ አካባቢዎች

ዋዜማ- በአማራና በትግራይ ክልል የይገባኛል ውዝግብ ባለበት የራያ አካባቢ እገታ፣ ዝርፊያና ግድያ እየተስፋፋ መሆኑንና ወጣቶችን አስገድዶ ለውትድርና መመልመልም እየተበራከተ መምጣቱን ዋዜማ ካሰባሰበችው መረጃ ማረጋገጥ ችላለች።  ዋዜማ ከአካባቢው ነዋሪዎች፣ ከተጎጂዎችና ቤተሰቦቻቸው…

የታደሰ ወረደ አመራር ውድቀት ገጥሞታል፤ አዲስ መንግስት መቋቋም አለበት ሲል የትግራይ አለማቀፍ ምሁራን ስብስብ ጥሪ አቀረበ

ዋዜማ- ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ የሚመሩት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ ውድቀት አጋጥሞታል ሲል የትግራይ አለማቀፍ የምሁራንና ባለሞያዎች ስብስብ አዲስ ባቀረበው የግምገማ ሪፖርት ወቀሳ አቀረበ፡፡ ዋዜማ የተመለከተችው ሪፖርቱ በአቶ ጌታቸው ረዳ አመራር…

የትግራይ ተቃዋሚዎች ክስተት ፤ ስምረትና ሹም ተምቤን

ዋዜማ- በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀስ “ሹም ተምቤን” የተሰኘ አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የቅድመ ምዝገባ ፍቃድ በማግኘት በምስረታ ሂደት ላይ መሆኑን ዋዜማ ሰምታለች፡፡ “ሹም ተምቤን ፓርቲ” ከምርጫ ቦርድ የምስረታ ፍቃድ…

በደቡብ ትግራይ ግጭት ተቀሰቀሰ

ዋዜማ- በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ትዕዛዝ የተሠጣቸው የታጠቁ ኃይሎች፣ በደቡባዊ ትግራይ የራያ አካባቢ አስተዳደራዊ መዋቅሮችን በኃይል ለመቆጣጠር መንቀሳቀሳቸውን ተከትሎ፣ ባካባቢው ግጭት መፈጠሩን ዋዜማ ሠምታለች፡፡ በርካታ የታጠቁ ኃይሎች ማክሰኞ፣ ሐምሌ 15፣ 2017…

የትግራይ “መንበረ ሠላማ” ጳጳሳት ወደ አዲስ አበባ እየመጡ ነው

ዋዜማ- ራሳቸውን ከሀገር አቀፉ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የነጠሉት የትግራይ የሀይማኖት አባቶች ጠቅላይ ሚንስትሩን ለማነጋገር ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑን ለዋዜማ ተናግረዋል። ራሳቸውን “መንበረ ሠላማ” ብለው የሚጠሩትና በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሄደውን ደም አፋሳሽ…

በአዲስ አበባ “የሻዕቢያ ተልዕኮ አስፈፃሚ” ናቸው የተባሉ 224 ስዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ዋዜማ- የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ብቻ 224 “የሻዕቢያ መንግሥት ተልዕኮ አስፈጻሚዎች” ናቸው ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ዋዜማ ከፀጥታና ደህንነት ምንጮች ስምታለች። ቢሮው፣…