ዋዜማ ራዲዮ- በምስራቅ ወለጋ ኬረሙ ወረዳ ነጭሎ በተባለ አካባቢ አስራ አንድ ሰላማዊ ሰዎች ተገደሉ።

ባለፈው ሀሙስ ዕኩለ ቀን የኦነግ ሼኔ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አስራ አንድ ሰዎች ሲገደሉ ከሀያ በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለዋዜማ ራዲዮ ገልፀዋል።

እስከ ዓርብ ከሰዓት በኋላ ድረስ የሟቾቹ አስከሬን አለመነሳቱን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

የኦነግ ሼኔ ታጣቂዎች በድጋሜ ጥቃት ሊያደርሱ ይችላሉ በሚል ነዋሪዎች ቀበሌውን ለቀው እየወጡ መሆኑንም ለዋዜማ ገልፀዋል።

በጉዳዩ ላይ መረጃ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ሀላፊዎች የችግሩን መከሰት አምነው ዝርዝሩን ከመናገር ግን ተቆጥበዋል።


በቅርቡ የመከላከያ ሀይል በኦነግ ሽኔ ታጣቂዎች ላይ የከፈተውን ሰፊ ዘመቻ ተከትሎ ታጣቂዎቹ ይዞታቸውን ለቀው ወደ ሌሎች አካባቢዎች እየሸሹ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። [ዋዜማ ራዲዮ]