Tag: Media

መንግስት ባልተለመደ መልኩ ለፋና ብሮድካስቲንግ እና ለዋልታ ዳጎስ ያለ የገንዘብ ድጋፍ እያደረገ ነው

ዋዜማ – በፓርቲ ንብረትነት ለሚታወቁት ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እና ለዋልታ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት ባልተለመደ መልኩ የፌደራሉ መንግስት  በርካታ መጠን ያለው ገንዘብ ድጎማ እያደረገላቸው መሆኑን  ዋዜማ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል። የሚድያ…

መስከረም አበራና ሰለሞን ሹምዬ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ዋዜማ ራዲዮ- የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ትናንት ረፋዱ ላይ ባዋለው ችሎት የዩትዩብ መገናኛ ብዙኀን ዝግጅት አቅራቢዋን መስከረም አበራን ጉዳይ ተመልክቷል። በዕለቱ መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዋ ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት እና አማራ ክልልን…

ብርሃን እና ሰላም ማተሚያ ቤት ያደረገው እስከ 80 በመቶ የደረሰ የህትመት ዋጋ ጭማሪ ለመገናኛ ብዙሀን አዲስ መሰናክል ሆኗል

ዋዜማ ራዲዮ- የመንግስት የልማት ድርጅት የሆነው ብርሃን እና ሰላም ማተሚያ ቤት በጋዜጣ አሳታሚ ደንበኞቹ ላይ ያደረገውን የዋጋ ጭማሪ የሚገልጽ ደብዳቤ ለደንበኞቹ የላከው መጋቢት2፤2014 ነው፡፡  ድርጅቱ የዋጋ ጭማሪውን በአንድ ጊዜ ላለመጫንም…

የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የምርመራ ጋዜጠኝነት መመሪያ እያዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ

ዋዜማ ራዲዮ– በኢትዮጵያ ግልጽና ተዓማኒነት ያለውና የምርመራ ጋዜጠኝነት በስርዓት ሊመራ የሚችል መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሃመድ ኢድሪስ ገለጹ፡፡ የዋዜማ ሪፖርተር ከፓርላማ እንደዘገበው የምርመራ ጋዜጠኝነት በጥሩ…

“ምን ልታዘዝ” የቴሌቭዥን ድራማ ቡድን አዲስ ስራ ይዞ እየመጣ ነው

ዋዜማ ራዲዮ- በፋና ቴሌቭዥን እና በዩቲዩብ ለተወሰኑ ወራት ቀርቦ በውዝግብ የተቋረጠው “ምን ልታዘዝ” ድራማ ተዋናዮች ደራሲና አዘጋጅ በአዲስ ድራማ ወደ ተመልካች ለመድረስ እየተሰናዱ መሆኑን ዋዜማ ከቡድኑ አባላት ስምታለች።“አስኳላ” የተሰኘ አዲስ…

የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር ከሀላፊነታቸው ተነሱ

ዋዜማ ራዲዮ- የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ወንድወስን አንዱዓለም ከሀላፊነታቸው መነሳታቸውን ዋዜማ ራዲዮ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች ስምታለች። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ድንቁ (ዶ/ር) ከቀናት በፊት በፈቃዳቸው ስልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል።…

የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዳይሬክተር ስልጣናቸውን ለቀቁ

ዋዜማ ራዲዮ- የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዳይሬክተር ጌታቸው ድንቁ (ዶ/ር) በሳምንቱ መጨረሻ በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸውን ዋዜማ አረጋግጣለች። ዳይሬክተሩ ለሁለት ዓመታት ያህል ተቋሙን መርተዋል። አሁን ስልጣን የለቀቁበትን ምክንያት ለጊዜው አላብራሩም። ይሁንና…

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ማስጠንቀቂያ ተሰጠው

ሕግ ተላልፈዋል የተባሉ የሳተላይት ስርጭቶችን በዘላቂነት ለማስቆም ጥረት እየተደረገ ነው ዋዜማ ራዲዮ- የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በቅርቡ ካስተላፋቸው ፕሮግራሞች ውስጥ የሙያ ስነ ምግባር ጉድለት ታይቶባቸዋል ፣ የህገ መንግስት ጥሰትም ተስተውሎባቸዋል…

የኢትዮጵያ መንግስት አመፅ ቀስቅሰዋል ያላቸውን ሁለት የሳተላይት የቴሌቭዥን ስርጭቶች አሳገደ

ዋዜማ ራዲዮ- ከሰሞኑ የድምፃዊ ሀጫሉ ሁንዴሳን መገደል ተከትሎ የተቀሰቀሰውን ማንነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት በመቀስቀስ ተሳትፈዋል የተባሉት ሁለት የትግራይ ክልል የቴሌቭዥን ጣቢያዎች ስርጭት ኢዩቴል(EutelSat) ከተባለው የፈረንሳይ ሳተላይ ላይ እንዲወርድ መደረጉን ተረድተናል።…