Tag: ETHIOPIA

ኦነግ ሸኔ አዲስ ዘመቻ ጀምሯል?

ዋዜማ- ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን፣ ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞኖች ከመንግሥት ወታደሮች ጋር ከወትሮው በተለየ መልኩ ተከታታይ ውጊያ እያካሄደ ስለመሆኑ ዋዜማ ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች  ካሉት ምንጮቿ…

በአማራ ክልል በእርግጥ መረጋጋት እየመጣ ነው?

ዋዜማ – በአማራ ክልል በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚደረጉት ውጊያዎች፣ አሁንም ተባብሰው መቀጠላቸውን ዋዜማ በኹሉም የክልሉ አካባቢዎች ባደረገችው ማጣራት ተገንዝባለች። ዐሥር ወራትን ባስቆጠረው የኹለቱ አካላት ግጭት በክልሉ…

የባንክ ተበዳሪ ነዎት? ወይም ለመበደር አስበዋል? እነዚህ አዲስ መመሪያዎች ይመለከትዎታል

ዋዜማ- የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንኮች ከቀውስ ይታደጋል፣ መረጋጋትም ያሰፍናል ያላቸውን አምስት አዳዲስ መመሪያዎች ይፋ አድርጓል። መመሪያዎቹ ከዚህ ቀደም የተወሰዱ ብድሮችንም ሆነ አዲስ የሚሰጡ ብድሮች ላይ ገደብ እና ተጨማሪ ተጠያቂነትን…

አልፋሽጋ ከሶስት ክረምት በኋላ ?

ዋዜማ- የፌደራሉ መንግስት ከትግራይ አማፅያን ጋር ጦርነት ላይ በነበረበት ወቅት የሱዳን ወታደሮች ድንበር ተሻግረው የኣኢትዮጵያ ይዞታ የነበሩ አካባቢዎችን መቆጣጠራቸው ይታወቃል። ከሶስት ዓመት ተኩል በኋላ ዋዜማ የድንበሩ አካባቢ ያለበትን ሁኔታ ለመመልከት…

ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችበትን ውዝግብ እንድታረግብ አሜሪካ ጠየቀች

ዋዜማ- የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ አንቶኒ ብሊንከን ቅዳሜ ዕለት የሶማሊያውን ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐመድን በስልክ ያነጋገሩ ሲሆን፣ ኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል እየተካረረ ያለው ውዝግብ መርገብ እንዳለበት አሜሪካ ፍላጎቷ መሆኑን ገልፀዋል።…

የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው ምን ይዟል?

ዋዜማ- የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መንግሥት፣ ለብዙ ጊዜያት ሲጠበቅ የነበረውን የፍትሕ ፖሊሲ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ማፅደቁ ተሰምቷል። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያፀደቀውን ይህን ከፍተኛ አገራዊ ትርጉም ያለው ፖሊሲ የተመለከተችው ዋዜማ፣ ለአንባብያኖቿ…

በራያ የተቋረጡ የህዝብ አገልግሎቶችን ለማስጀመር ፌደራል መንግስትና የትግራይ ክልል ውይይት እያደረጉ ነው

ዋዜማ- የትግራይ ክልል ጊዜያዊ  አስተዳደር በቅርቡ በተቆጣጠረው የራያ አካባቢ መስረታዊ የህዝብ አገልግሎቶችን ለማስጀመር ከፌደራል መንግስቱ ጋር ውይይት እያደረገ መሆኑንና በመግባባት እየሰራ እንደሆነ ለዋዜማ ተናግሯል። በቅርቡ በሕወሓት ታጣቂዎች እና በአካባቢው ሚሊሻዎች…

በፒያሳ ለኮሪደር ልማት የፈረሱ ሰፈሮችን ጨምሮ በከተማው በርካታ ቦታዎች የሊዝ ጨረታ ወጣ

ዋዜማ- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ ከአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዝየም ፊት ለፊት ለኮሪደር ልማት በሚል የፈረሱ ሰፈሮችን ጨምሮ ከ250 በላይ በሚሆኑ…

የጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ስራ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሊደረግ ነው

ዋዜማ- በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ታሪክ ከአምስት አስርት ዓመታት በኋላ የውጭ ባለሀብቶች በሀገር ውስጥ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ላይ እንዲሰማሩ የሚፈቅድ የህግ ማእቀፍ ተጠናቆ ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ዋዜማ ከተለያዩ ምንጮች ስምታለች። ለኢትዮጵያ…

ጠቅላይ ሚንስትሩ የተቃዋሚ  ፓርቲ አባላትን ለውይይት ጋበዙ፣ ፓርቲዎቹ ስልጠናም ይወስዳሉ ተብሏል

ዋዜማ- የተቃዋሚ  ፓርቲ መሪዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ውይይት ለማድረግ ቀጠሮ መያዛቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች።  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሁሉንም አገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ ፖለተካ ፓርቲዎችን ለማወያየት ወደ አዲስ…