ፍቅር የተራበው አብሪ ኮከብ… ለምን ሲሳይ

እድል ይሁን አጋጣሚ ባይታወቅም እሱም ይሁን ወላጆቹ ሳይፈልጉት ይህ ሰው በሰው አገር የወላጅና የቤተሰብ ፍቅር እየራበው አድጉዋል። ያም ሆኖ ተወልዶ ባደገበት አገር ባልተጠበቀ ሁኔታ ታላቅነትን ያለማንም ድጋፍ ተጎናጽፉዋል። ለምን ሲሳይ…

የደቡብ ሱዳን ጦርነት ጦስና የኢትዮጵያ ውልውል

በአዲስ አበባ ሲካሄድ የሰነበተው የመጨረሻ የደቡብ ሱዳን ሰላም ድርድር እነሆ ሰኞ ዕለት ያለ ውጤት ተበትኗል፡፡ “ኢጋድ ፕላስ” በተሰኙት አደራዳሪዎች በተቀመጠላቸው ቀነ-ገደብ ዕለት ተቃዋሚው ሬክ ማቻርና ሶስተኛ ወገን ተደራዳሪዎች የሚባሉት ከእስር…

የምስጢር ውስልትናው መንደር እየታመሰ ነው-ስምዎን ይፈልጉ

ከትዳራቸው ውጪ ለሚወሰልቱ አገልግሎት ሲሰጥ የከረመው አሽሊ ማዲሰን የተባለ ድረገፅ በመጠለፉ በርካቶች ሰው “መሳይ በሸንጎ” የሚስብላቸውና ገመናቸውን አደባባይ ያዋለ ክስተት ተፈጥሯል። 40 ሚሊየን የሚቆጠሩ ደንበኞች የስም ዝርዝርና የክሬዲት ካርድ መረጃ ይፋ…

የሙስሊሞች ጉዳይ (ክፍል 2)

በመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላቱ ላይ የተሰጠው ብይን በሰላማዊ ትግሉ ላይ የአቅጣጫ ለውጥ ይከስት ይሆን? የብዙዎቻችን ጥያቄ ነው። እያደገ ከመጣው የዓለም ትስስር አንፃር የአክራሪነትና ፅንፈኝነት አደጋ በኢትዮዽያ ሙስሊሞች ውስጥ ስር እየሰደደ…

የጀነራሎቹ ቤት

የመከላከያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (METEC) ከሀገሪቱ ሀብት እየዘገነ ራሱን ያስፋፋል እንጂ ስባሪ ሳንቲም ወደ መንግስት ካዝና አስገብቶ አያውቅም። እጅ ባጠረው ጊዜ መንግስት ይደጉመዋል፣ የሚተዳደረው በወታደራዊ ህግ ሲሆን ኦዲት አያውቀውም።…

ኢህአዴግ መቶ ፐርሰንቱ የምርጫ ውጤት መዘዝ አለው እያለ ነው

ኢህአዴግ መቶ ፐርሰንቱ የምርጫ ውጤት ለተቃዋሚዎች ሰበብ ሆኗል፣ ከህዝቡ ጋር ጥርጣሬ ውስጥ ከቶናል፣ የምዕራባውያን ጫናም በርትቶብናል ሲል ገመገመ። ሰፊ የህዝብ ግንኙነትና የፕሮፓጋንዳ ስራ ዕቅድም አውጥቷል። ውጤቱ የአመፅና የጠመንጃ መንገድ ለመረጡት…

የደቡብ ሱዳን ተፈላሚዎች በመጨረሻዋ ሰዓት

ከግጭቱ ማግስት ጀምሮ በአፍሪካ ቀንዱ በይነ-መንግስታት ድርጅት ኢጋድ አማካኝነት ከ15 በላይ የተኩስ አቁም ስምምነቶች ቢደረሱም አንዳቸውም ፍሪያማ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡ ካለፈው ዓርብ ጀምሮ ደግሞ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው ድርድር ሁለቱ ወገኖች…

ኦንላይን የአማርኛ መዝገበ ቃላት ከእጃችን የሚገባበት ጊዜ ተቃርቧል

የፈረንጁን ቋንቋ አብዝተው ለማይደፍሩ ኢትዮዽያውያን ፈተናቸውን ሊያቀልላቸው ይችላል የተባለውና በአማርኛና በሌሎች የሀገራችን ቋንቋዎች የተዘጋጀ የኦንላይን መዝገበ ቃላት ለአገልግሎት ሊበቃ መቃረቡን ሰምተናል። ይህ መዝገበ ቃላት የኦንላይን መረጃ ፍለጋን በተመለከተ አዲስ በር…