Month: March 2018

ዶ/ር አብይ አህመድ ከኃይለማርያም ደሳለኝ በምን ይለያሉ?

ዋዜማ ራዲዮ- ገዥው ግንባር መዋቅራዊና ፖለቲካዊ ለውጦችን ባያካሂድም የኦሕዴዱ ሊቀመንበር ዶክተር አብይ አሕመድ ወደ ጠቅላይ ሚንስትርነቱ መምጣታቸው በብዙ ወገኖች ዘንድ በተለይም በኦሮሞ ብሄር ተወላጆች ዘንድ የደስታ እና ተስፋ ስሜት ፈጥሯል፡፡ በርግጥ…

የሞያሌውን ግድያ እንዲያጣራ የተቋቋመው ቡድን ማጣራቱን እንዲያቆም ታዘዘ

ዋዜማ ራዲዮ- በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ሞያሌ ከተማ በመከላከያ ሰራዊት አባላት ስለተገደሉት ዜጎች ጉዳይ እንዲያጣራ የተሰየመውና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፈፃፀም የሚከታተለው መርማሪ ቦርድ የማጣራት ተልዕኮውን እንዲያቋርጥ መታዘዙን የዋዜማ ምንጮች…

ገዥው ግንባር በኤርትራ ላይ አቋሙ ምንድነው?

ዋዜማ ራዲዮ- በኤርትራ ላይ የሚከተለውን የውጭ ፖሊሲ እየከለሰ መሆኑን ደጋግሞ ሲገልጽ የከረመው ኢሕአዴግ-መራሹ መንግስት እንደገና ውስጣዊ የጸጥታና ፖለቲካ ቀውሱን ባለፈው ሳምንት በኤርትራ መንግስት አሳቧል፡፡ ባለፈው መጋቢት 8 የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ…

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በሁለት አቅጣጫ በመንግስት ላይ ጥቃት ሰነዘርኩ አለ

ዋዜማ ራዲዮ- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ባለፉት ቀናት በደቡብ ምዕራብ ሞያሌ እና በምዕራብ ወለጋ አካባቢዎች በመንግስት ወታደሮች ላይ ጥቃት አድርሻለሁ ሲል አስታወቀ። በአስመራ ዋና መቀመጫውን ያደረገው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር የማዕከላዊ ኮሚቴ…

ሶማሊያና ጅቡቲ ከኢትዮጵያ ጋር ኩርፊያ ላይ ናቸው

ዋዜማ ራዲዮ- ኢትዮጵያ የዐረብ ኤምሬትሱ ዱባይ ፖርትስ (Dubai Ports) ና ሶማሊላንድ የበርበራ ወደብን በጋራ ለማልማትና ለመጠቀም የደረሱበት ስምምነት ሞቃዲሾን አስቆጥቷል። የሀገሪቱ ፓርላማም ስምምነቱን ውድቅ አድርጎታል፡፡ ፓርላማው ከአንድ ተቃውሞና ከአንድ ድምጸ…

የኃይሌ ገብረስላሴ የንግድ ተቋም በኮማንድ ፖስቱ ትዕዛዝ ተዘጋ

ከአዘጋጁ፡ ይህ ዜና አዳዲስ መረጃ ትክሎበታል፣ በስተ መጨረሻው ላይ ተመልክቷል። ዋዜማ ራዲዮ- የታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ኃይሌ ገብረስላሴ ንብረት የሆነ  ሪዞርት በአስቸኳያ ጊዜ አዋጁ ስበብ በኮማንድ ፖስቱ እንዲዘጋ መደረጉን የዋዜማ ሪፖርተሮች…

የቀለም አብዮት ተረት ተረት እንደገና!

ዋዜማ ራዲዮ- ሰሞኑን ኢሕአዴግ-መራሹ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ሽፋን አድርጎ ህዝባዊ አመጹን ከቀለም አብዮት ጋር የሚያገናኝ ትርክት በማምጣት በዴሞክራሲያዊ ማሻሻያ ላይ በተጣለው የተስፋ ጭላንጭል ላይ በረዶ ቸልሶበታል፡፡ ከዐመታት በፊት የሀገሪቱ…

የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር በመጪው ሳምንት አዲስ አበባ ይመጣሉ

ዋዜማ ራዲዮ- የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ሪክ ቲለርሰን በመጪው ሳምንት ኢትዮጵያን ጨምሮ አምስት የአፍሪቃ ሀገራትን ይጎበኛሉ። የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሐሞስ ዕለት ይፋ እንዳደረገው ሚንስትሩ ኢትዮጵያን ጨምሮ ኬንያ ጅቡቲ…