PM Abiy Ahmed- FILE


ዋዜማ ራዲዮ- ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ ነገ (ሰኞ) የካቲት 9 ቀን 2012 ዓ. ም እየተወሳሰበ የመጣውን የሕዳሴው ግድብ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ መጥራታቸውን ዋዜማ ተረድታለች።


ስብሰባው የሚደረገው በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ በተከታታይ በዋሽንግተን ሲደረግ የነበረውን ድርድር ተከትሎ ነው።

ድርድሩ ያልተቋጨ ቢሆንም አሜሪካ በመሪዎች ደረጃ ስምምነት እንዲፈረም ለማስቻል የውጪ ጉዳይ ሚንስትሯ ማይክ ፖምፒዮ በቀጣዮቹ ቀናት አዲስ አበባ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድን አግኝተው ያነጋግራሉ።


ኢትዮጵያ ስምምነቱን ለመፈረም የተሰማማች ቢሆንም ገና ያላለቁ የህግና የቴክኒክ ጉዳዮች አሉ።ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ የአሜሪካ የልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ከመድረሱ አስቀድሞ አቋም ለመያዝ አስቸኳይ የምክክር ስብሰባ መጥራታቸውን ተረድተናል። [ዋዜማ ራዲዮ]