ዋዜማ- በአማራና በኦሮሚያ ክልል በመንግስትና በአማፅያን መካከል የቀጠለው ግጭት የበርካታ ዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ ከማስተጓጎሉም በላይ ቀላል የማይባሉ ዜጎችን ህይወትም እየቀጠፈ ነው። መንግስት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግጭት በነበረባቸው አካባቢዎች መረጋጋት መስፈኑን ለማስመስከር ይመስላል ባለስልጣናቱ የልማት ስራ እንዲጎበኙ ሲያሰማራ ስንብቷል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይም መረጋጋት መስፈኑን ለማስረገጥ ወደ ነቀምት ያመሩት ከሳምንታት በፊት ነበር። በተመሳሳይ ወቅት በአማራ ክልል የአባይ ድልድይንም መርቀዋል።

በእርግጥ መንግስት እንደሚለው አማፅያኑ ተዳክመው መረጋጋት መስፈን ጀምሯል ? ብለን ግጭት በነበረባቸው አካባቢዎች ባደረግነው ማጣራት ያገኘነው መረጃ ስለ እውነቱ የተወሰነ ግንዛቤ ይሰጣል ብለን እናምናለን። አንብቡት

የአማራ ክልልን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ የተመለከተው የመስክ ዘገባ በዚህ ማስፈንጠሪያ ይመልከቱት

የኦሮሚያ ክልልን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ የተመለከተው የመስክ ዘገባ በዚህ ማስፈንጠሪያ ይመልከቱት