ዋዜማ ራዲዮ- በኢትዮጲያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ የጤና ተቋም ስራተኛች ቁጥር 97 ደርሷል ፣ በአብዛኛዎቹ በሁለት ሳምንት ውስጥ የተያዙ ናቸው፡፡

በኢትዮጲያ የኮረና ቫይረስ ከገባበት መጋቢት ወር በኃላ ስርጭቱ ባለፉት ሁለት ሳምታት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑንና በቫይረሱ የሚያዙ የጤና ተቋም ሰራተኛች ቁጥርም እያሻቀበ እንደሆነ የጤን ሚንስትሯ ሊያ ታደሰ ከሚመለከታቸው ባለሙያዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ተናግረዋል። ባለፉት ሁለት ሳምንታት ብቻ 81 የሚሆኑ የጤና ተቋም ባለሙያዎች በቫይረሱ እንደተያዙ ይፋ ከተደረገው መረጃ ለመረዳት ችለናል፡፡

ቫይረሱ ከተገኘባቸው መካከል 91 የሚሆኑት በአዲስ አበባ የሚገኙ ናቸው፡፡ በቫይረሱ ከተያዙት የጤና ተቋም ሰራኞች መካከል 55 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው፡፡አብዛኞቹ ሰራተኛች ምንም አይነት የበሽታው ምልክት ያልታየባቸው ሲሆኑ ነገር ግን ቫይረሱ እንደተገኘባቸው በምርመራ ተረጋግጧል፡፡

እስካሁን ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ንክኪ ነበራቸው ተብለው የተለዩ እና እራሳቸውን አግልለው የነበሩ የጤና ባለሙያውች ቁጥር 2340 ደርሶል ከነዚህ መካከል 1721 የሚሆኑት ተጋላጭ የነበሩት መጋቢት ወር ላይ ነው፡፡

የጤና ባለሙያዎቹ በዘውዲቱ ሆስፒታል ክትትል ሲያደርጉ የቆዩ በሆንም አሁን ቁጥራቸው እየጨመረ ስለመጣ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ እየተዘዋወሩ ነው፡፡

ለህክምና ተቋማት የሚያስፈልጉ ራስን የመከላከያ ቁሳቁሶች እጥረት እንዳለ ሆኖ የአጠቃቀም እና የጥንቃቄ ጉድለቶች መስተዋላቸውንም ከተደረገው ሙያዊ ውይይት ለመገንዘብ ችለናል፡፡

ግንቦት 21 ቀን 2012 ከኢትዮጲያ ሕክምና ማህበር የወጣ ደብዳቤ ምን ያህል የጤና ለሙያዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ እንደሆኑ፤ በቫይረሱ እነደተጠቁ ወደ ለይቶ ማቆያ እንደገቡ አህዛዊ መረጃ ከመንግስት እንዲሰጠው ጠይቆ ነበር ፡፡ ይህ ጥያቄው የተነሳው በበሽታው የሚያዙ የጤና ባለሙያውች ቁጥር እየጨመረ ስለመጣ ክፍተቱ የቱ ጋር በግልፅ እንዳለ ለመረዳት እና የስራ ላይ አደጋን ለመቀነስ የሚቻልበትን መንገድ ለማፈላለግ ያለመ መሆኑን የኢትዮጲያ ሕክምና ማህበር ያብራራል። [ዋዜማ ራዲዮ]