Author: wazemaradio

የኢትዮጵያና የኤርትራ ግጭት ዛሬም ቀጥሏል፣ ሁለቱም ሀገሮች ተጨማሪ ጦር እያንቀሳቀሱ ነው

ዋዜማ ራዲዮ- ቅዳሜ ምሽት የተቀሰቀሰው የድንበር ግጭት ዛሬ ሰኞ ድረስ ቀጥሎ ማርፈዱን ከአካባቢው የተገኙ የዋዜማ ምንጮች ገለፁ። የኢትዮጵያ መንግስት የኮምንኬሽን ጉዳዮች ሚንስትር ጌታቸው ረዳ በሁለቱ ሀገራት መካከል ውጊያ መደረጉንና ውጊያው…

ኬንያ የሶማሊያ ስደተኞችን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እየተጣደፈች ነው

የኬንያ መንግስት ግማሽ ሚሊዮን ያህል የጎረቤት ሀገር ስደተኞችን ያስጠለለባቸው ግዙፎቹን ስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎች ባንድ ዓመት ውስጥ ለመዝጋት የወሰነው ባለፈው ወር ነው፡፡ ከዚህ ውሳኔ በኋላ አዲስ ሱማሊያዊያን ስደተኞችን እንደማይቀበል ይፋ አድርጓል፡፡…

ኤርትራ በኢትዮጵያ መንግስት ጥቃት ተከፍቶብኛል ስትል ከሰሰች

ይህ ዘገባ በኤርትራ ወገን ስላለው ሁኔታ የሚያብራራ ነው።ከኢትዮጵያ ወገን ያሰባሰብነው መረጃ ከስር ባለው ማስፈንጠሪያ ይመልከቱት። ዋዜማ ራዲዮ- የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስትር ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት በፆረና ግንባር ወረራ ፈፅሞብኛል…

በኢትዮ-ኤርትራ ድንበር ግጭት መቀስቀሱ ተሰማ

ዋዜማ ራዲዮ- በኢትዮ-ኤርትራ ድንበር በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ከትናንትና ጀምሮ የተኩስ ልውውጥ እየተካሄደ እንደሆነ እና ግጭቱም ወደለየለት ጦርነት የመቀየር አዝማሚያ እንዳለው ምንጮች ለዋዜማ ገለጹ፡፡ የተኩስ ልውውጡ የተቀሰቀሰው በጾረና እና ዛላምበሳ ግንባሮች…

የአገር ሰው ጦማር- አዲሳባ ገዢዎቿን ብቻ ሳይሆን ዜጎቿን እየመሰለች ነው

ሰኔ፣ 2008 ተጻፈ፣ በሙሔ ሐዘን ጨርቆስ እንዴት ናችሁ የዋዜማ ታዳሚዎች? ከትናንትና ወዲያ ጋሽ አበራ ሞላ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ጋር ቆሞ ሲያስነጥስ አየሁት፡፡ እነዚህ ሰዎች ቆሻሻ የትም እየደፉ አሳበዱት፡፡ ቁመቱ ከምን ጊዜውም ረዝሞ…

[በነገራችን ላይ]- ኦጋዴን ከአድዋ ጦርነት እስከ ዛሬ

የኦጋዴን ሶማሌዎች በኣአድዋው ጦርነት ከፊት ነበሩ። ዛሬ በኢትዮጵያ ዋና የጦርነት ማዕከል ከሆኑ አካባቢዎች ኦጋዴን ይጠቀሳል። ከአሰከፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ባሻገር ክልሉ ድህነት ብርቱ በትር ካሳረፈባቸው የሀገራችን ክልሎች አንዱ ነው። የሶማሌ…

የኢህአዴግ “ጥላ” የምርምርና ጥናት ተቋማት

በተለምዶ “ቲንክ-ታንክ” ተብለው የሚታወቁትትን የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከላት በሀገራችን መስርቶ በመምራት የህወሃቱ ሰው አቶንዋይ ገብረአብ ቀዳሚ ናቸው፡፡ ምንም እንኳ ኢትዮጵያ አንጋፋና ስመ-ጥር የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከላት ባይኖሯትም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ…

የአገር ሰው ጦማር: በአሉላ ጫካ የሚሰራው የባለስልጣናቱ “ቅንጡ” ቤት እየተጠናቀቀ ነው፡ ጎብኝቼው ተመለስኩ

የተከበራችሁ የዋዜማ ራዲዮ ታዳሚዎች- የጦማሬ አንባቢዎች! የተከበራችሁ ጭቆናን የሚቋቋም ደንዳና ትከሻ ባለቤቶች! የተከበራችሁ የ40-60 ተመዝጋቢዎች! የተከበራችሁ የ80-20 ነባር ተመዝጋቢዎች! የተከበራችሁ የ90-10 የድሀ ድሃዎች! ክቡራትና ክቡራን! ኮንዶሚንየም እስኪደርሳችሁ የኢዮብን ትዕግስት ባስናቀ…

የአገር ሰው ጦማር: ግንቦት 20ን ከልቡ የሚያከብራት ማን ነው?

  እንዴት ናችሁልኝ የዋዜማ ታዳሚዎች? እኔ ያው ደኅና ነኝ፡፡ እነሆ ጣሊያን ከሄደ ስንትና ስንት ዓመቱ! እኔ ግን ለምን እንደሆን አላውቅም ቅኝ እየተገዛሁ ይመስለኛል፤ የገዢዎቼን ልደት ለ25ኛ ጊዜ ተንበርክኬ ማክበሬ የፈጠረው ስሜት…

“ፈተናዎቹን በእጃችን ያስገባነው ከሶስት ሳምንት በፊት ነበር” የኦሮሞ ተቃውሞ አስተባባሪዎች

የፈተና ወረቀቱ የተሰረቀበትን ቦታና ተሳታፊ ግለሰቦችን ለመለየት ሁለት አስቸኳይ ስብሰባዎች ተደረገዋል (ዋዜማ)-ካለፈው ህዳር ወር ጀምሮ በመላው ኦሮሚያ የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ የሚደግፉ አስተባባሪዎች እና አራማጆች ጉዳዩን ወደ ሌላ ምዕራፍ የሚያሸጋግር እርምጃ በዛሬው…